ለንግድ ላልሆነ ዓላማ የሚቀርብ የጀነቲክ ሀብት አርክቦት ማመልከቻ (በጀነቲክ ሀብት ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ጥናትና ምርምር ለማካሄድ)
በጀነቲክ ሀብትና የማኅበረሰብ ዕውቀት አርክቦት የማኅበረሰብ መብቶች አዋጅ ቁ. 482/1998 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 1 እና በደንብ ቁ.169/2001 አባሪ II መሠረት ጀነቲክ ሀብትን ለጥናትና ምርምር ዓላማ ለማርከብ የሚፈልግ አመልካች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች አሟልቶ ማመልከቻውን ሊያቀርብ ይገባል፡፡
- ጠቅላላ መረጃ
- የአመልካቹ ተቋም ስምና አድራሻ፣
- የተቋቋመበት ሰነድ (ተቋሙ የተቋቋበት ሕግ ወይም የምዝገባ ሠርተፊኬት፣ እንዲሁም ተቋሙ በኢትዮጵያ የሚገኝ በይነ-መንግሥታዊ ተቋም ከሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሠራ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያደረገው ስምምነት ኮፒ)፣
- ዝርዝር መረጃ
- የጀነቲክ ሀብት ናሙና ከሀገር ለማስወጣት የሚቀርብ ሕጋዊ ማመልከቻ ደብዳቤ፣ ደብዳቤው በመ/ቤቱ የበላይ ሀላፊ የተፈረመ፣ የመዝገብ ቁጥር የያዘ እና ህጋዊ ማህተም ያረፈበት
- የተመራማሪው ስም በደብዳቤው መጠቀስ አለበት
- የተመራማሪው/አጥኚው አግባብነት ያለው መታወቂያ፣
- በማኅተምና ፊርማ የተረጋገጠ የምርምር / የጥናት ንድፈ ኃሳብ፣
- የምርምሩ ዓላማ፣ የሚጠበቅ ውጤት፣
- የጀነቲክ ሀብቱ ናሙና ዓይነትና መጠን (በግራም፣ በኪሎ ግራም፣ በቁጥር፣… ፣ወዘተ)፣
- ለማርከብ የተፈለገው የጀነቲክ ሀብት ሳይንሳዊ ስያሜ (ቢቻል እስከ ዝርያ ደረጃ ድረስ የተለየ)
- የጀነቲክ ሀብቱ የሚገኝበት ቦታ፣
- ጀነቲክ ሀብቱ ሊውል የታሰበበት ጠቀሜታ በዝርዝር፣
- የታሰበው ምርምር ዓይነትና ጥልቀት፣
- ጥቅም ላይ የሚውለው የባለሙያና የመሣሪያ ዓይነት፣
- ምርምሩ የሚፈጀው ጊዜና ከምርምሩ የሚጠበቀው ውጤት፣
- የጀነቲክ ሀብቱ መጀመሪያና በቀጣይነት ሊወሰድ የሚችልባቸው ቦታዎች፣
- ምርምሩ ወይም ከፊሉ ምርምር በኢትዮጵያ ውስጥ የማይካሄድ ከሆነ፣ ሊካሄድ የማይችልበት ምክንያት፣
- ምርምሩ ለኢትዮጵያ የሚያስገኘው ጥቅም፣
- የጀነቲክ ቁስ ማስተላለፊያ ስምምነት ሰነድ (ከኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ድረ-ገፅ http://www.ebi.gov.et/gm-access/gm/ላይ የሚገኝ)
- በ 5 ዋና ቅጂዎች የተዘጋጀ፣
- በጀነቲክ ሀብቱ ተጠቃሚ አካላት በአግባቡ ተሞልቶ የተፈረመበትና ማኅተም የተደረገበት፣
- መረጃዎቹ በአግባቡ የተሟሉለት (የምርምር ዓላማ፣ የሚጠበቅ ውጤት፣ የጀነቲክ ሀብት ናሙና ዓይነትና መጠን፣ የጀነቲክ ሀብት ሳይንሳዊ ስያሜ፣ የጀነቲክ ሀብቱ የሚወሰድበት አገር)፣
- የማረጋገጫ ደብዳቤ ማቅረብ (ከኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ድረ-ገፅ http://www.ebi.gov.et/gm-access/letter-of-assurance//ላይ የሚገኝ)( Assurance letter for Assurance letter CNA(Comp.Nat.Auth.) (.doc))
- ምርምሩ/የጥናት ሥራው ከኢትዮጵያ ውጭ እንዲካሄድ በሚፈቀድበት ጊዜ የአርክቦት አመልካቹ ምርምሩን የደገፈው እና/ወይም ምርምሩ የሚካህድበት ተቋም ምርምሩ በሚካሄድበት ወቅት የአርክቦት ግዴታዎችን እንሚያከብሩና እንደሚያስከብሩ የሚገልጽ ደብዳቤ ማስላክ ይኖርበታል፡፡
- የደብዳቤው ይዘት የያዘ ፎርማት በድህረ- ገጽ ያለውን መሰረት በመ/ቤቱ የበላይ ሀላፊ የተፈረመ፣ የመዝገብ ቁጥር የያዘ እና ህጋዊ ማህተም ያረፈበት መሆን አለበት
- አርክቦት አመልካቹ የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሀገሩ ወይም ከሚኖርበት ሀገር አግባብነት ያለው ባለሥልጣን አመልካቹ የሚኖርበትን የአርክቦት ግዴታዎች በዚያ ሀገር የሚያስከብርና የሚያስፈጽም መሆኑን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርበታል::
- የደብዳቤው ይዘት የያዘ ፎርማት በድህረ- ገጽ ያለውን መሰረት በመ/ቤቱ የበላይ ሀላፊ የተፈረመ፣ የመዝገብ ቁጥር የያዘ እና ህጋዊ ማህተም ያረፈበት መሆን አለበት
- የጀነቲክ ሀብት ናሙና ቅጂና ናሙናውን የሚገልፅ መረጃ
የአርክቦት አመልካቹ በተጠየቀ ጊዜ ከሚወስደው የጀነቲክ ሀብት ላይ ናሙናውን ከሚገልፀው መረጃ ጋር ለኢንስቲትዩቱ ወይም ኢንስቲትዩቱ በሚሰይመው ተቋም ውስጥ ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡